አገልግሎቶች | የሲዳማ ክልል የመንግስት ልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን
የሰው ሀብት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት
ዳይሬክቶሬቱ የሚሰጣቸው ዋና ዋና አገልግሎቶች:-
- የተቋሙን ሠራተኞች መንግሥት ባወጣው የምዘና ስርዓት መሠረት በየወቅቱ እንዲመዘኑ የማድረግ አገልግሎት
- በመንግሥት ሠራተኞች መመሪያዎችና ደንቦች መሠረት ልዩ ልዩ የቅጥር፣ የደረጃ ዕድገት፣ ዝውውር፣ የዲስፕሊን፣ የቅሬታ ማስተናገጃ አገልግሎት
- አግባብነት ያላቸው ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙና ተግባራዊ እንዲሆኑ የማድረግ አገልግሎት
- አዲስ ለሚቀጠሩ ሠራተኞች ስለ መንግሥት መመሪያዎችና ደንቦች እንዲሁም ተቋሙ ስለተቋቋመበትና ስለሚጠበቅበት ውጤት ስልጠና መስጠት
- ለመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና እንድያገኙ የማድረግ አገልግሎት
- የተለያዩ የድጋፍ ደብዳቤዎችን የመስጠት አገልግሎት
- ጡረታ ለሚወጡ መንግስት ሰራተኞች ሁኔታ የማመቻቸት አገልግሎት
- አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የሰው ሀብት ሥራ አመራርን የተመለከቱ መመሪያዎች እንዲከለሱና አዳዲስ ጥናት እንዲጠኑ የማድረግ አገልግሎት
- መልካም ተሞክሮዎችን በማጣጣም ዳይሬክቶሬቱ የሚመራበትን አዳዲስ አሰራሮች በመቀመር ማስፋፋት
- የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ ሰርኩላሮችና አግባብነት ያላቸው መመሪያዎችን ተፈጻሚነታቸውን የመከታተል አገልግሎት
- ልዩ ልዩ ጥቅማ ጥቅሞችና አገልግሎቶች ሳይዛቡ ሥራ ላይ እንዲውሉ የማድረግ አገልግሎት
- የሠራተኞች የግል ማህደሮች ተሟልተውና ዘመናዊ ሆነው እንዲያዙ ክትትል የማድረግ አገልግሎት
- የሰው ኃይል እቅድ መረጃዎች እንዲሰበሰቡ፣ እንዲደራጁ ተተንትነው እንዲጠናቀሩ ማድረግ
የዳይሬክቶሬቱ የሰራተኛ ደረጃ:-
| የዳይሬክቶሬቱ ስም | የሰው ሀብት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት |
|---|---|
| የሰራተኞች ብዛት (ወንድ) | ___ |
| የሰራተኞች ብዛት (ሴት) | ___ |
| አጠቃላይ ሰራተኞች ብዛት | ___ |


